Sunday, June 23, 2013

በዛብህ ከ" ግጥም እና እኔ "

በዛብህ
እናትና አባቴ በስለት ወልደውኝ
ለስለታቸው መልስ ለካህኑ ሰጡኝ
የሰጣቸው ጌታ ከቅይሩ ሊያኖረኝ
ባካባቢው ካህናት ቅኔን አስተማረኝ
አሐዱ አምላክ ብዬ ዳዊቴን ደግሜ
ሰዓታት ወረቡን ቅዳሴውን ቆሜ
በለጋው ዕድሜዬ ጥበብን ተክኜ
ላፈሩኝ ወላጆች ከልብ ለተሳሉት
ላያዩኝ ላይድሩኝ መልሰው ለሰጡት
ለነሱ አልሆን ብዬ ከሱ ተጠግቼ
እንደ ጧፍ በራሁኝ ታየሁኝ ጎልቼ
የኔ ጎልቶ መውጣት ስለቱን ፈተነው
የውስጤን ሊለካ አየኝ ፊት አውራሪው
ከጌታው መኖሪያ ከባለፀጋው ቤት
አለች እፀ በለስ ነብሴ የምትሰጋት
ውበትዋያማረ ሰብል ነው እኔ የማልነካው
ባለፍኩበት ቁጥር ውስጤን ከስር የሚያናጋው
ፊደል ባስቆጠርኩኝ እንዳባቷ ዛዝ
ታዝብኝ ጀመረች የፍቅርን ትኩሳት
እኔ የስለት ልጅ እሷ እፀ በለስ
ድሮ ተዘግቶብኝ ሁሉ ማይቀመስ
የአጥሩ መብዛት ከዘሮቿ ደጅ
ምንም ብንካጀል የለን አማላጅ
የሁለታችንም ልብ ነጎደ ሌላለም
እያወቅነው የስለቱን የጌታውን ሕመም
ለሕዝብ አልተመቸ ለፈጠረኝ ጌታ
ከቀዬ ሲያባረኝ የስለት ከርታታ
ዲማ ጊዮርጊስም እንቢ አለ ይኼንን መዋጋት
በለስ ጌታ የድሃ ሰው ስለት ክልክል የነገስታት
ፍቅሬ ቢጠና አገር አቆራርጦ
አፈናቅሎ ጣላት እሷን አስቆጥቶ
ገደልን ፈንቅለን ተርበን ተጠምተን
ስለትን እረግመን ሸሸን ነገሥታቱን
መቃብር ሊወርደው ፍቅረ መውደዳችን
ባላሰብነው መንገድ ባልጠፋበት ጊዜ
የፈጠረን ጌታ ለፍቅር ለሐዘን ኑዛዜ
ሰጠን ያችን ዕለት የመቃብር ፍቅር
ይዘነው እንድንሄድ ሁሉንም በክብር::

ሔለን ካሳግጥም እና እኔ” (2005)

Tuesday, June 18, 2013

ድጋፋችሁ አይለየን

ውድ የዚህ ድረገጽ ጎብኝወች ይህ ድር ጀማሪ እንደ መሆኑ መጠን ከእናንተ አስተያየት ይፈልጋል ስለዚህ ለድሩ እድገት ያላችሁን የ ሀሳብ ድጋፍ አትንፈጉን ብለን ለማሳሰብ እንወዳለን

Saturday, June 15, 2013

ምርጥ ምርጥ አባባሎች

ብሂ
ሌላ መንገድ በመፈለግ ጊዜህን አታጥፋ መንገድ በፊትህ ነው:: ተነስቶ መራመድ ያንተ ፋንታ
ነው::
/አውግሰጢኖስ
ልብህን ብሩህ አድርገው ዓለምን የምትመለከትበት መስኮት ነውና::”
ጆርጅ በርናርድ ሾው
ሕይወት ራሷን ላለመጣል ከምትቀይሳቸው አቅጣጫዎች በአንዱ ውስጥ ማለፍ የግድ ነው::”
ጥሩ ወይም መጥፎ የሚባል ነገር የለም፣ አስተሳሰባችን የሚፈጥረው እንጂ::”
ዊልያም ሺክስፒር
ለሌሎች ካላሰብንና የምንችለውን ካላደረግንላቸው ከደስታ ምንጮች አንዱን እንዳደረቅን
እንገንዘብ::” ሬይ ሊመን ዊልበት
ብዙ ሰዎች የሚደሰቱት ራሳቸውን ለደስተኝነት ባዘጋጁት መጠን ነው::”
አብርሃም ሊንከን
መፍራት ያለብን ራሱን ፍራቻን ብቻ ነው::”
ፍራንክሊን ሩዝቬልት
ጨለማን ሲረግሙ ከመኖር አንዲት ቁራጭ ሻማ መለኮሱ ይበጃል::”
ራልፍ ዋልደ ኢመርሰን
ፍርሃትህን ለራስህ በጉያህ ሸሽግ ወኔህን ግን ከሌሎች ጋር ተካፈል::”
ሮበርት ሉዊስ ስቲቭንሰን
ለራሱ በቂ ነገር እያለው በጋራ መጠቀምን የማይሻና በማኅበር ለመኖር እራሱን የማያስገድድ ሰው
ቢኖር ሰው ሳይሆን አውሬ መሆን አለበት::”
አርስቶትል
ዛሬ ቀን ከሚገጥምህ ነገር ጋር ራስህን ለማስማማት ታገል እንጂ እኔ እንደፈለግሁት ካልሆነ
አትበል::”
አብርሃም ሊንከን
አንድን ነገር በማወቅና በመረዳት መካከል ትልቅ ልዩነት አለ::”
ቻርለስ ካታሪንግ

ወርቃማው ህግ
ክርስትና
እንግዲህ ሰዎች ሊያደርጉላችሁ የምትወዱትን ሁሉ እናንተም ደግሞ እንዲሁ
አድርጉላቸው ሕግም ነቢያትም ይህ ነውና:: (ማቴ 7÷12)
እስልምና
ለራሳችሁ የምትመኙትን ለሌሎችም እንዲሆን እስካልተመኛችሁ ድረስ በትክክል
አላመናችሁም:: (የነብዩ መሐመድ ተግባራትና ንግግሮች)
የአይሁዶች እምነት
አንተ የምትጠላውን ነገር በባልጀራህ ላይ አታድርግ ይህ ነው እግዚአብሔር
ለሙሴ የሰጠው ሕግ ሲጠቃለል:: (ሒላል ታልሙድ ሻባት 31)
የባሃኢ እምነት
በአንተ ላይ ሊጫንብህ የማትፈልገውን በሌላ ላይ አታድርግ በራስህም ላይ
እንዲደርስብህ የማትሻውን ለማንም አትመኝ:: (ባሀኡላህ)
ቡዲሂዝም
ራስህን የሚጎዳ የሚመስልህን ነገር በሌሎች ላይ አታድርግ::
ሒንዱዝም
አንተ ላይ ቢደረግ የሚያስከፋህ ከሆነ አንተም በሌሎች አታድርግ የተግባር ሁሉ
ማጠቃለያ ይህ ነውና:: (ማኅበራታ 51517)
ጃኒዝም
ማንም ሰው ለራሱ እንዲደረግለት የሚሻውን እርሱም እንዲሁም በዓለም ዙሪያ
ላሉ ፍጡራን ሁሉ ያድርግ:: (ማሃቪራ ሱትራክሪታንጋ)
ሲኪሂዝም
ለማንም ባይተዋር አይደለሁም ማንም ለእኔ ባይተዋር አይደለም የሁሉም ወዳጅ
ነኝ:: (ጉሩ ግራንትዝ ሳሂብ ፒጂ.1299)
ዩኒታሪያኒዝም
ሁላችንም አካል የሆነበትን የፍጥረታት አንድነትና ትስስር በጽኑ እንደግፋለን
እንዲሁም ልዩ አክብሮት እንዲሰጠው እንተጋለን:: (የዩኒታሪያን መርሆ)
ታኦዝም
ጎረቤትህ ሲያተርፍ አንተ እንዳገኘህ ቁጠር ጎረቤትህ ሲከስር አንተ እንዳጣህ
አድርገህ ውሰድ:: (ቲአይ ሻንካ ካንዩንግ ፒዮን 213-218)
ኮንፉሺያኒዝም
የመልካም ሥነ ምግባር መሠረት ማጠቃለያ የሆነ አንድ ቃል ነው እሱም
ሩህሩህ መሆን በአንተ ላይ ሊደረግ የማትፈልገውን በለሎች ላይ አታድርግ::
(ኮንፍሺየስ አናሌክትስ 15.23)
ዞሮአስትሬይኒዝም
አንተን የሚጎዳ ነገር ሁሉ በሌሎች ላይ አታድርግ:: (ሻያስት-ና-ሻያስት 13.29)
ኔቲቭ ስፒሪቹአሊቲ
የኛ ሕልውና የሚረጋገጠው የምድራችን ተፈጥሮ ይዞታ ሲጠበቅ ነው:: (ቺፍ ዳን ጆርጅ)


ኢንተርፌዝ ፒስ ቢዩልዲንግ ኢንሽየቲቭ